ራዕይ
ባህላዊ ተፈጥሮአዊና ታሪካዊ ሀብቶቹን የሚያለማ፣ የሚንከባከብና የሚጎበኝ ኀብረተሰብ በመፍጠር በ2ዐ2ዐ ዓ/ም አዲስ አበባን በዓለም ተመራጭ ከሆኑ የአፍሪካ 5 ዋና ዋና የቱሪስት መዳረሻና፣ የባህል ማዕከል ከተሞች መካከል አንዷ ማድረግ፡፡
ተልዕኮ
የከተማዋን ባህላዊ፣ ታሪካዊና ተፈጥሯዊ ሀብቶች የሚወድ፣ የሚጠብቅ፣ የሚያበለፅግና ወደ ልማት ኃይልነት የሚቀይር የተለወጠ ትውልድ በመፍጠር፣ ባህልና ኪነ-ጥበብን ዋነኛ የልማት ሀይል በማድረግ እና የቱሪስት መስህቦችን በማስተዋወቅ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ነው፡፡ ይህንንም ለማሳካት ግንዛቤ ማስጨበጥ፣ በማስተዋወቅ፣ አስተባብሮ በማሳተፍ፣ የመሪነት ሚና ይጫወታል፡፡
ዋና ዋና ተግባራት
- ቴአትር፣ የባህልና ዘመናዊ ሙዚቃ ማቅረብ፣ ፊልሞችን ማሳየት
- አገራዊ የፊልም ማዕከል በማቋቋም ፊልሞችን መስራት ዶክመንተሪ ፊልም መስራት፣ የሬዲዮ ፕሮግራሞችን ማሰራት
- የብሔር ብሔረሰቦች እሴቶችን ጠብቆ ማቆየትና ማስተዋወቅ
- የሙያ ማረጋገጫ ሰርተፊኬት መስጠትና የሙያ ምዝገባ ማካሄድ፣ የፊልምና የቴአትር ማሳያ ፈቃድ መስጠት/ ለውጭና ለውስጥ/
- በከተማ ወስጥ በኪነ-ጥበብ ዘርፍ ስልጠና የሚሰጡ ተቋማት መቆጣጠርና ፈቃድ መስጠት
- የኪነ-ጥበብ መረጃዎችን በተሟላና በሳይንሳዊ መንገድ ስብሰባ ማደራጀት፣ ማሰራጨት፣ ከተማ አቀፍ የኪነ-ጥበብ ፌስቲቫሎች ማዘጋጀት
- ከአለማቀፍና ከክልሎች ጋር ኪነ-ጥበብ አኳያ ግንኙነት መፍጠር
- የህዝብ ቤተ-መፃህፍት የሚቋቋሙበትንና ሚስፋፉበትን
- ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን፣ አሉታዊ ተጽእኖ ያላቸውን መጤ ባህሎችንና የለውጥ እንቅፋት የሆኑ አመለካከቶችን በመዋጋት የአመለካከትና የአሠራር ለውጥ ማምጣት
- ቅርሶችን ማጥናት መመዝገብ፣ መጠበቅ፣ እንዲመዘገቡ ማድረግ ለቅርሶች ክትትልና ጥበቃ እንክብካቤ ማድረግ፣
- ሙዚየሞችን ማደራጀት መምራትና አገልግሎት ላይ እንዲውሉ ማድረግ
- የከተማውን እምቅ የቱሪዝም ሀብት በሀገርና በአለም አቀፍ ደረጃ ጥራቱን በጠበቀና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ማስተዋወቅና ገበያ መፍጠር
- ዘመናዊ በቴክኖሎጂ የተደገፈ የቱሪስት መረጃ ማዕከል መፍጠር