በገቢ ታክስና ግብር አሰባሰብን አስመልክቶ በህብረተሰቡ እየታየ ያለውን የአስተሳሰብ ለውጥ የሚያግዙ የተለያዩ ኪነጥበብ ስራዎችን ለህዝብ ማድረሱን የአዲስ አበባ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ አስታወቀ፡፡
በቢሮው ጥር 15/2004 ዓ.ም ላይ በስሩ የሚገኙ 3 ዋና የስራ ሂደቶች 4 ቴአትር ቤቶች ፣ የአዲስ አበባ ቤተ-መጽሐፍት ወመዘክርና የአዲስ አበባ ሙዚየም እንዲሁም የአስሩም ክፍለ ከተማ ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት ኃላፊዎች በተገኙበት የቢሮው የ6 ወር አፈጻጸም ግምገማ ሲካሄድ እንደተገለጸው አገራችን ካስቀመጠችው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ መሳካት በኪነ-ጥበብ ዘርፍ ሁለንተናዊ ለውጥ ለማምጣት በተደረጉ እንቅስቃሴዎች በህዳሴው ግድብ ላይ የሚያተኩሩ ፣ የሴቶችንና ወጣቶችን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ እንዲሁም በትምህርት ጥራት ፣ ሽፋንና ፍትሃዊነት ላይ ያተኮሩ ዝማሬዎች ፣ ድራማና ሙዚቃዊ ድራማዎች በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች ለህዝብ መድረሳቸው ተገልጻDል፡፡
የቢሮው ኃላፊ አቶ ገብረፃዲቅ ሀጎስ እንደገለጹት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በከተማዋ ህብረተሰብ እየታየ ያለውን የስራ ባህል እድገት እና የቁጠባ ባህል ጅምር እንቅስቃሴዎችን እንዲሁም ለከተማችን ዘላቂ እድገት ወሳኝ ሚና የሚጫወተውን የገቢ አሰባሰብ ስርዓት በኪነ-ጥበብ ለማገዝ ቢሮው እቅድ ነድፎ ወደ ተግባር መግባቱን አስታውሰው ባለፉት 6 ወራትም የከተማዋን ሁለንተናዊ እድገት በመደገፍና ቢሮው ከቆመለት ሁነኛ ዓላማ አንፃር በከተማዋ የብሔር ብሔረሰቦች ባህል ግንባታ ላይና የቅርሶች አጠባበቅና አያያዝ ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራቱን አብራርተዋል፡፡
የቢሮው ኃላፊ አያይዘውም በመልካም ስነ መግባር የታነፁና ሙስናን የሚፀየፍ ዜጋ ለመፍጠር እንዲያግዝ ከፌዴራል ስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ጋር በመተባበር ለ75 የሴክተሩ
አመራሮችና ሰራተኞች ስልጠና ከመስጠቱም ባሻገር በተለያዩ ክፍለ ከተማዎች ከፖሊስና ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር በመሆን የህገወጥ ቅጅ እንቅስቃሴን ለመከላከል የሚያስችል ስኬታማ ውይይቶች ተደርገዋል ብለዋል፡፡
በውይይቱ ከተሳተፉት መካከል አቶ ኩራባቸው ደነቀና ወ/ሮ አዜብ ከበደ የራስ ቴአትርና የህጻናትና ወጣቶች ቴአትር ቤት ስራ አስኪያጆች በውይይቱ ላይ እንደተናገሩት ባለፉት 6 ወራት አመርቂ ተግባራት የተከናወኑ ቢሆንም ከህብረተሰቡ የጥበብ ፍላጎት አንጻር ቴአትር ቤቶቹ በቀጣይ 6 ወራትም የተሻለ ተግባራት ለማከናወን የእቅድ መርሃ ግብር አዘጋጅተው ወደ ተግባር ለመግባት ቅድመ ሁኔታዎች እየተመቻቹ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
የአድዋን ድል 114 ዓመት በዓል አስመልክቶ የተዘጋጀው ፕሮግራም በአዲስ አበባ ቲያትርና ባህል አዳራሽ የተካሄደ፡፡ በእለቱ የባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ አቶ ገብረፃዲቅ ሃጎስ በክብር እንግድነት ተገኝተዋል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ቢሮ በበጀት 2ዐዐ2 ዓ/ም የመጀመሪያው 6 ወር እቅድ አፈፃፀም የተሻለ ውጤት ላስመዘገቡ የሥራ ሂደቶች የክፍለ ከተማ ጽ/ቤቶች እንዲሁም በ BSC እና BPR ጥናት ላይ ለተሳተፉ ሙያተኞች የማበረታቻ ሽልማት ሰጠ፡፡
Addis Ababa Culture and tourism is a division of Addis Ababa City Administration