በኢትዮጵያ ታሪካዊና ባህላዊ ቅርሶችን የመጠበቅና የመንከባከብ እንቅስቃሴ የተጀመረው ኢትዮጵያዊያን ሣይንቲስቶች ከፈረንሣይ አቻዎቻቸው ጋር የአርኪዎሎጂ ጥናት ማድረግ በጀመሩበት ወቅት ነበር፡፡ በወቅቱ በአርኪኦሎጂ ዙሪያ የተደጉት ጥልቅ ጥናቶች ከጥናቱ የሚኙትን የአርኪኦሎጂ ውጤቶችን በሙዚየም ለማከማቸትና ለእይታ ለማቅረብ ሙዚየሙን መገንባት በእጅጉ አስፈላጊ መሆኑ ስለታመበት ነው፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሙዚየም በ1944 ዓ.ም ተመሠረተ፡፡ ሙዚየሙ ሲመሰረት ጥቂት ቅሪቶችን በማሰባሰብና ስለአገሪቱ ብሔረሰቦች ክብረ በዓላት የሚያንፀባርቁ ቁሳቁሶችን በማሰባሰብ ነበር፡፡ ሙዚየሙ በጊዜ ሂደት እየተሻሻለ እያደገ ሄደ፡፡ በዚህ ሂደትም ውስጥ ሙዚየሙ አሁን ያለበትን ሕንፃ ለመገንባት በቅቷል፡፡
ሙዚየሙ በአራት ክፍሎች የተከፋፈለ ነው፡-
- የመጀመሪያው ክፍል ስለሰው ልጅ አመጣጥ ቅድመ ታሪክ የሚያሣይ ሲሆን በዚህ ክፍል የሉሲ አጽምና ቀደምት የሰው ልጆች የሚጠቀሙባቸው የድንጋይ መሣሪያዎችን ይዟል፡፡
- በሁለተኛው ክፍል ታሪካዊና አርኪኦሎጂካዊ ግኝቶች የሚገኙበት ሲሆን በዚህ ክፍል ከአክሱም በፊት እስከ 16 ክ/ዘመን ያለውን ገጽታ ያሣያል፡፡
- በሶስተኛው ክፍል የብሔር ብሔረስቦችን ባህልና የክብረ በዓላት ሥርዓት፣ ጊጣጌጦች የሚንፀባረቁበትና የብሔር ብሔረሰቦች ባህል የሚታይበት ነው፡፡
- በአራተኛው ክፍል ዘመናዊ የሥነ ስዕል ጥበብ ሲገኝ በሥሩም በተለያዩ ኢትዮጵያውያን የተሣሉና የተቀረፁ ሥዕልና ቅርሳ ቅርሶች ይገኛሉ፡፡
ሙዚየሙ ለጐብኚዎች ምቹ ነው፡፡ ምክንያቱም በእያንዳንዱ ቅርስ /እቃ ላይ ስለእቃው ዝርዝር መረጃ ይገኛል፡፡ ከዚህም ባሻገር ሙዚየሙ ከመደበኛው ሥራው በተጨማሪ ሙዚየሙን ለመጐብኘት ለሚፈልጉ ተማሪዎችና ጐብኚዎች ልዩ የጉብኝት ፕሮግራም ያዘጋጃል፡፡ ሌላው በሙዚየሙ የሚሰጠው አገልግሎት ቱሪስቶች የሚገዟቸውን ታሪካዊና ባህላዊ ቅርሶች በሕገ ወጥ መንገድ ወደ ውጪ እንዳይወጣ ይከላከላል፣ ይቆጣጠራል፣ በቅርሶች ላይ ፍተሻ ያደርጋል፡፡
አድራሻ፡- አምስት ኪሎከብሉቶፕ ሬስቶራንት ፊት ለፊት
ስ.ቁ፡- +251.11 111 9131/ ext 715ዐ
የጉብኝት ሰዓት፡- ከሰኞ - እሁድ /ከሕዝብ በዓላት በስተቀር/ ከ2፡3ዐ - 11፡3ዐ ሰዓት